ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ከእማዋ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ዛሬ ጥር 27 ቀን 2018 ዓ.ም ተፈራረመ።
ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ከእማዋ ሾፒንግ ኩባንያ ጋር አብሮ በመሥራቱ ደስተኛ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በተለይም ባንኩ በኢትዮጵያ በፍጥነት በማደግ ላይ ባለው የንግድና የፋይናንስ ዘርፍ ላይ እያደረገ ያለውን ጉልህ የሆነ አወንታዊ አስተዋጽኦ አጠናክሮ እንደሚቀጥል እና እማዋ ሾፒንግ ኩባንያ ትልቅ የቢዝነስ ርዕይ ይዞ ወደ ሥራ የገባ በመሆኑ ባንካችንም የድርጅቱ ርዕይ ስኬታማ እንዲሆን በቁርጠኝነት የሚሠራ መሆኑ በመርሐ ግብሩ ላይ ተሰምቷል፡፡
የእማዋ ሾፒንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ባለቤትና ጄኔራል ማኔጀር አቶ ሰለሞን አየነው በበኩላቸው ኩባንያው ከንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ጋር በተለያዩ ዘርፎች አብሮ ለመሥራት በመቻሉ እጅግ ደስተኛ መሆኑን ገልጸው እማዋ ሾፒንግ ከባንኩ ጋር የጋራ የሚያደርገውን የማንነት (identity) ብራንድ ፈጥሮ ኢንተርናሽናል ስታንዳርድ ያለው ካምፓኒ ለመፍጠር ያለመውን ርዕይ ለማሳካት የሚሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡
እማዋ ሾፒንግ በርካታ ወጣቶች ተጠቃሚ የሚሆኑበት ትልቅ ኩባንያ መሆኑን ያመለከቱት አቶ ሰለሞን ገበሬው፣ ታዳጊ ማንፋክቸሪንግ ተቋማትና ልዩ ልዩ አቅራቢ ድርጅቶች ተጠቃሚ የሚሆኑበት መሆኑን አመልክተዋል፡፡
በፊርማ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የባንኩ እና የእማዋ ሾፒንግ ኩባንያ ከፍተኛ የማኔጅመንት አካላት የተገኙ ሲሆን ባንካችንን በመወከልም የባንኩ ቺፍ ሪቴይልና ኤስኤምኢ ባንኪንግ ቺፍ ኦፊሰር አቶ ሙሉቀን ደምሴ የፊርማ ሥነ ሥርዓት አካሄደዋል፡፡




