Internet Banking
Internet Banking

ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባዘጋጀው የኢትዮጵያ የፋይናንስ ፎረም – 2025 ላይ በመሳተፍ “ንብ ተራ” በሚል ስያሜ አገልግሎቱን ለታዳሚዎች እያስተዋወቀ ይገኛል፡፡

ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዘጋጅነት ዛሬ በአዲስ አበባ የሳይንስ ሙዚየም በይፋ በተከፈተው ፎረም ላይ በመሳተፍ አዳዲስ የዲጂታልና ነባር መደበኛ አገልግሎቶቹን “ንብ ተራ” በሚል ስያሜ ለተከበሩ የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት አቶ ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የብሔራዊ ባንክ ዋና ገዥ የተከበሩ አቶ ማሞ ምህረቱ፣ ለሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናትና የተለያዩ ባንኮች ዋና ሥራ አስፈጻሚዎች በተገኙበት አስተዋውቋል፡፡

 

የፋይናንስ ፎረሙ ለሁለት ቀናት ማለትም ግንቦት 07 እና 08 ቀን 2017 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን ባንኮች፣ ኢንሹራንሶች፣ አነስተኛ የገንዘብ ተቋማት፣ የውጭ ምንዛሬ ቢሮዎች፣ የልማት አጋሮች እና ሌሎችም የታደሙ ሲሆን እርስዎም በፎረሙ እንዲሳተፉና እንዲጎበኙን ተጋብዘዋል፡፡

***
ይሠሯል ከልብ፣ እንደ ንብ!

<p> <b>  <span style="color: #8B5E3C;">Nib International</span>   <span style="background: linear-gradient(to right, #8B5E3C, #FFA500); -webkit-background-clip: text; color: transparent; font-weight: bold;">     Bank   </span></b> </p>

Nib International Bank

Committed To Services Excellence

Share this post with

Recent Posts

You May Also like

Reports

Jobs