Internet Banking
Internet Banking

ባንካችን የዒድ-አል-አድሃ (አረፋ በዓል)ን ምክንያት በማድረግ በማዕከላዊ አዲስ አበባ፣ በሆሳዕናና በሐዋሳ ዲስትሪክቶች ስር በሚገኙ ቅርንጫፎቹ የማርኬቲንግ ንቅናቄን አስጀምሯል።

ንቅናቄው እስከ አረፋ በዓል ዋዜማ በተለያዩ ከተሞችና ቅርንጫፎች እየተስፋፋ ይከናወናል። በዚህም የነባር ደንበኞች የተቀማጭ ገንዘብ መጠንን የማንቃት፣ አዳዲስ አካውንቶችን የማፍራት እና የገፅታ ግንባታ ሥራ የማጎልበት ተግባራት ይከናወናሉ።

 

”በአዲስ መንፈስ ለላቀ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል የለውጥ እንቅስቃሴውን አጠናክሮ የቀጠለው ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በአዳዲስ የሥራ ሃላፊዎችና አሰራሮች ታግዞ ይበልጥ ወደ ደንበኞቹ እየቀረበ ይገኛል።

የማርኬቲንግ ንቅናቄውን እንቅስቃሴ በከፊል የሚያሳዩ ምስሎችን በዚህ ማስፈንጠሪያ https://www.nibbanksc.com/gallery/ መመልከት ይችላሉ፡፡

ኢድ ሙባረክ!

***

ይሠሯል ከልብ፣ እንደ ንብ!

 

NIB BANK

NIB BANK

Committed To Services Excellence

Share this post with

Recent Posts

You May Also like

Reports

Jobs