Internet Banking
Internet Banking

ንብ ባንክ የሲስተም ትስስር የትግበራ ውል ስምምነት ተፈራረመ

ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ፣ ከአዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር መሠረታዊ የኅብረት ሥራ ማኅበር ጋር የኮር ባንኪንግ ሥራዎችን የሚያስተሳስር የሲስተም ትስስር (System Integration) የትግበራ ውል ስምምነት አቡዋሬ በሚገኘው የማኅበሩ ዋና መሥሪያ ቤት ህዳር 23 ቀን 2015 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተፈራረመ፡፡

የሲስተም ትስስር ትግበራው፣ የማኅበሩ አባላት ወርሃዊ የቁጠባ ሂሣባቸውንም ሆነ የብድር ክፍያቸውን በባንኩ በሚገኘው የማኅበሩ ሂሣብ ሲያስገቡ በፍጥነት (Real Time) አዋጭ ወደሚገኘው ሂሣባቸው ይተላለፋል፡፡ በተጨማሪም የባንኩንና የኅብረት ሥራ ማኅበሩን ሂሣብ ለማወራረድ የሰው ጣልቃ ገብነት በሌለበት ማከናወን የሚያስችል ሲሆን፣ ይህም ለሌሎች የዲጂታልና ኤሌክትሮኒክ ማበልጸግ ሥራዎች በር መክፈቱንና አመቺነትን የፈጠረ መሆኑም በፊርማ ሥነ ሥርአቱ ላይ ተገልጿል፡፡
የመግባቢያ ስምምነቱን፣ አቶ ልዑልሰገድ ንጉሤ የባንካችን የስትራቴጂና ትራንስፎርሜሽን ምክትል ፕሬዚዳንት እና አቶ ሰለሞን ወሌ የአዋጭ የኮር ባንኪንግና ሶፍትዌር ማስፋፊያ ኃላፊ ፈርመዋል፡፡

ይሠሯል ከልብ እንደ ንብ!

ዌብ ሳይት፡ www.nibbanksc.com
የፌስቡክ ገፃችን፡ https://bit.ly/3C33uM1
የኢንስታግራም ገፃችን፡ https://bit.ly/3p8OUuy
ሊንክዲን፡ https://bit.ly/3bJUhgG
የቴሌግራም ቻናላችችንን ለመቀላቀል፡ https://bit.ly/3SBzNYd

የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችንን Like, Follow እና Share ማድረግዎን አይርሱ!

#nib #nibbank #budget #friday #nibbankofficialpage #banksinethiopia #fintech #bank #finance #ethiopia #ethiopian

NIB BANK

NIB BANK

Committed To Services Excellence

Share this post with

Recent Posts

News

ባንካችን ያጋጠመውን ጊዜያዊ ችግር በአጭር ጊዜ ለመፍታት ከደንበኞች፣ ከሠራተኞችና ከባንኩ

Read More

You May Also like

Reports

Jobs