“የላቀ የደንበኞች አገልግሎት፣ ለጋራ ስኬት!” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ የሚገኘው የማርኬቲንግ ንቅናቄ አካል የሆነው የአገልጋይነት ቀንን ምክንያት በማድረግ የባካችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሄኖክ ከበደን ጨምሮ ከፍተኛ የማኔጅመንት አካላት ዛሬ ጳጉሜ 04/2017 ዓ.ም በአዲስ አመት ዋዜማ ሙሉ ቀን እናንተ ደንበኞቻችንን ለማገልገል በተመረጡ ቅርንጫፎች በመገኘት ሙሉ በሙሉ የባንኩን የኦፕሬሽንና ተዛማጅ ሥራዎችን በመስራት ደንበኞቻችንን በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡
እርስዎም አጋጣሚውን ተጠቅመው ወደ ተለያዩ ቅርንጫፎቻችን ጎራ በማለት በባንኩ የሥራ ኃላፊዎች የሚሰጠውን የባንክ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ስንጋብዝዎ በታላቅ ደስታ ነው፡፡







