ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ከጎዛም ቴክኖሎጂስ ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ዛሬ ህዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም በባንኩ ዋና መ/ቤት ተፈራረመ።
በመግባቢያ ስምምነቱ መርሐ ግብር ላይ የተገኙት የባንኩ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ አቶ ሄኖክ ከበደ፣ ከጎዛም ቴክኖሎጂስ ጋር የተደረገው ስምምነት ባንኩ ሥራ ላይ ያዋለውን አዲሱን የሦስት ዓመት ስትራቴጂ ዕቅድ እና የአምስት ዓመት ፍኖተ ካርታ በቴክኖሎጂ በማገዝ ስኬታማ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦና እገዛ እንደሚኖረው አመልክተዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የጎዛም ቴክኖሎጂ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ጀነራል ማናጀር አቶ ናርዶስ መአዛ በበኩላቸው ከንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ጋር በጋራ ለመሥራት በመስማማታቸው ደስተኛ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን ስምምነቱ ዓለም የደረሰበትን የቴክኖጂ ውጤቶችን በመጠቀም በተለይም በዳታ አናሊቲክስ እና በዳታ ሞደርናይዜሽን እና ሌሎች ዘርፎች ዙሪያ ከባንኩ ጋር በመሥራት ለውጥ ለማምጣት እንደሚሠሩ ገልጸዋል፡፡
የጎዛም ቴክኖሎጂስ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን፣ በዳታ ሞደርናይዜሽን፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በሪስክ ማኔጅመንት፣ በአይቲ ኢንፍራስትራክቸርና አፕሊኬሽን እንዲሁም በፊንቴክ ኢኖቬሽን ዙሪያ የተለያዩ ሥራዎች የሚሠራ ዓለም አቀፍ ተቋም እንደሆነ በመርሐ ግብሩ ተመልከቷል፡፡
***
ይሠሯል ከልብ፣ እንደ ንብ!




