ባንኩ በጅማ ከተማ ለሚኖሩና ገቢያቸው አነስተኛ ለሆነ የማኅበረሰብ ክፍሎች የትንሣኤ በዓል መዋያ ድጋፍ በጅማ ደ/መ/ቤ/ ክርስቲያን በመገኘት ድጋፍ አድርጓል።
በመርሐግብሩ ላይ በጅማ ደብረ መዌ መድሐኒያለም ቤተክርስቲያን የደብሩ ካህናት እንዲሁም የጅማ ዲስትሪክት ዳይሬክተር እና የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ድጋፉ ተደርጓል።
በመጨረሻም የደብሩ ካህናት ባንኩ ላደረገው ድጋፍ በቤተክርስቲያኗ ስም ምስጋና አቅርበው የእንኳን አደረሳቹህ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ድጋፍ የተደረገላቸው ወገኖችም ባንኩ ላደረገላቸው የቁሳቁስ ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ባንኩ የጀመረው የትንሳኤ በዓል ማኅበራዊ ኀላፊነት የመወጣት ተግባር በሌሎች አካባቢዎችም ተጠናክሮ ይቀጥላል ።





