ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በወልቂጤ ከተማ
የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ገቢያቸው አነስተኛ ለሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች ድጋፍ አደረገ።
በመርሃ ግብሩ ላይ የባንኩ ወልቂጤ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ ገብረማርያም እንደገለፁት ባንኩ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ በርካታ ተግባራት እያከናወነ እንደሚገኘ ጠቁመው በቀጣይም መሰል ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አመልክተው ለድጋፉ መሳካት የተባበሩትን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር አካላትን በማመስገን ለእምነቱ ተከታዮች መልካም የትንሳኤ በዓል እንዲሆንላቸው ከወዲሁ በመመኘት ድጋፍ አበርክተዋል።
ድጋፍ የተደረገላቸው ወገኖችም ባንኩ ባደረገላቸው ድጋፍ ደስተኛ መሆናቸውን በመጥቀስ ለተደረገላቸው የቁሳቁስ ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ባንኩ የጀመረው የትንሳኤ በዓል ማኅበራዊ ኀላፊነት የመወጣት ተግባር በተለያዩ አካባቢዎችም ዛሬም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተጠቁሟል።




